Surah Al-'alaq ( The Clot )

Surah Al-'alaq ( The Clot ) - Amharic Aya count 19

አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡
Share