Surah Al-A'la ( The Most High )

Surah Al-A'la ( The Most High ) - Amharic Aya count 19

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
Share