Surah Al-Mutaffifin (Those Who Deal in Fraud)

Surah Al-Mutaffifin (Those Who Deal in Fraud) - Amharic Aya count 36

ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
Share