Surah At-Takwir ( The Overthrowing )

Surah At-Takwir ( The Overthrowing ) - Amharic Aya count 29

ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
Share