Surah Abasa ( He frowned )

Surah Abasa ( He frowned ) - Amharic Aya count 42

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
Share