ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡