Surah An-Nazi'at ( Those who Pull Out )
Surah An-Nazi'at ( Those who Pull Out ) - Amharic Aya count 46
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡