መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?