Surah Al-Muddaththir ( The One Enveloped )
Surah Al-Muddaththir ( The One Enveloped ) - Amharic Aya count 56
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡