Surah Al-'adiyat ( Those That Run )

Surah Al-'adiyat ( Those That Run ) - Amharic Aya count 11

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡
Share